Saturday, 08 July 2017 13:10

“ኢትዮጵያን አትንኩ” የሙዚቃ ቪዲዮ ዛሬ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የክብር ዶ/ር አርቲስት ጥላሁን ገሰሰ ልጅ ዳንኤል ጥላሁን ገሰሰ “ኢትዮጵያን አትንኩ” የተሰኘው አዲስ ነጠላ ዜማና ቪዲዮ ክሊፕ ዛሬ ከምሽቱ 1፡00 ጀምሮ በካፒታል ሆቴል ይመረቃል። ድምፃዊ ዳንኤል ጥላሁን ከዚህ ቀደም ‹‹አባቴ ጥላዬ›› እና ‹‹እኔ ወይስ አንቺ›› የተሰኙትን የአባቱን ዘፈኖች አሻሽሎ መዝፈኑ ይታወሳል፡፡ በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የተለያዩ ኪነ-ጥበባዊና የመዝናኛ ፕሮግራሞች ለታዳሚው መዘጋጀቱንም የሀብል ሚዲያና ማስታወቂያ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሚልኪያስ ጌታቸው ጨምረው ገልፀዋል፡፡

Read 1674 times