የክብር ዶ/ር አርቲስት ጥላሁን ገሰሰ ልጅ ዳንኤል ጥላሁን ገሰሰ “ኢትዮጵያን አትንኩ” የተሰኘው አዲስ ነጠላ ዜማና ቪዲዮ ክሊፕ ዛሬ ከምሽቱ 1፡00 ጀምሮ በካፒታል ሆቴል ይመረቃል። ድምፃዊ ዳንኤል ጥላሁን ከዚህ ቀደም ‹‹አባቴ ጥላዬ›› እና ‹‹እኔ ወይስ አንቺ›› የተሰኙትን የአባቱን ዘፈኖች አሻሽሎ መዝፈኑ ይታወሳል፡፡ በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የተለያዩ ኪነ-ጥበባዊና የመዝናኛ ፕሮግራሞች ለታዳሚው መዘጋጀቱንም የሀብል ሚዲያና ማስታወቂያ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሚልኪያስ ጌታቸው ጨምረው ገልፀዋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና