ማይና ፕሮሞሽንና ኢንተርቴይመንት ከኢትዮጵያ ሆቴል ጋር በመተባበር በጋራ የሚያዘጋጁት ሰባተኛው ዙር ‹‹ህብረ-ትርኢት›› የኪነ ጥበብ ምሽት የፊታችን አርብ ከቀኑ 11፡30 ጀምሮ ይካሄዳል፡፡ በምሽቱ ወግ፣ ግጥም በጃዝ፣ አጭር ኮሜዲ ተውኔትና ሙዚቃ የሚቀርብ ሲሆን አንጋፋና ወጣትየኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ አዘጋጁ ማይና ፕሮሞሽንና ኢንተርቴይመንት ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡
Monday, 10 July 2017 00:00
‹‹ሕብረ- ትርኢት›› የኪነ- ጥበብ ምሽት ይካሄዳል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና