Monday, 17 July 2017 13:24

ኬንያ የፓርላማ አባላትን ደመወዝ በ15% ልትቀንስ ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

- አንድ የፓርላማ አባል በወር 10, 640 ዶላር ይከፈለዋል
- የግል ቤትና መኪና መግዣ የ257,400 ዶላር ብድር ይሰጠዋል
የኬንያ መንግስት የሰራተኞች ክፍያ ወጪውንለመቀነስ ሲል የፓርላማ አባላትን ወርሃዊ ደመወዝ  በ15 በመቶ ለመቀነስ ማቀዱን የዘገበው ቢቢሲ፤የአገሪቱ የፓርላማ አባላት ከፍተኛ ደመወዝ ከሚያገኙ የአለማችን ህግ አውጪዎች ተርታ ኬንያ የፓርላማ አባላትን ደመወዝ
በ15% ልትቀንስ ነው እንደሚሰለፉ ዘግቧል፡፡የኬንያ የፓርላማ አባላት በወር 7 ሺህ 200 ዶላር ደመወዝ ያገኙ እንደነበር ያስታወሰው
ዘገባው፤ የአገሪቱ መንግስት የያዘው አዲስ እቅድ ደመወዛቸውን በ15 በመቶ ከመቀነሱ በተጨማሪ፣በየሰበብ አስባቡ ያፍሱት የነበረውን ዳጎስ ያለ ውሎ አበልና ጥቅማጥቅም እንደሚያሳጣቸውም ገልጧል።አዲሱ ውሳኔ የመንግስት ባለስልጣናትን ደመወዝና ጥቅማጥቅሞች በከፍተኛ ሁኔታ
የሚቀንስ ነው ያለው ቢቢሲ፤ ከዚህ ቀደም የወር ደመወዛቸው ከ16 ሺህ ወደ 14 ሺህ ዶላር ዝቅ የተደረገባቸው የአገሪቱ ፕሬዚዳንትም በአዲሱ ህግ ሌላ ቅናሽ እንደሚደረግባቸው አመልክቷል፡፡በአገሪቱ አማካይ ወርሃዊ ገቢ 150 ዶላር ብቻ መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፤ የሚመለከተው የአገሪቱ ኮሚሽንም የሌሎች አገራትን ተሞክሮ በመገምገምና የፓርላማ አባላቱ ይህን ያህል ገንዘብ ማግኘታቸው አግባብ አለመሆኑን በማመን ቅናሽ እንዲደረግበት መወሰኑን ጠቅሶ፣ የደመወዝ ቅናሹም በመጪው ነሃሴ ወር መጀመሪያ የሚካሄደውን ብሄራዊ ምርጫ ተከትሎ ተግባራዊ ይደረጋል መባሉን አስረድቷል፡፡የኬንያ የፓርላማ አባላት ከ7 ሺህ 200 ዶላር ደመወዝ በተጨማሪ ከሚያገኙዋቸው ጥቅማጥቅሞች መካከልም፣ የ67 ሺህ 400 ዶላር የግል መኪና መግዣ ብድር፣ ለቤት መግዣ የሚውል የ190 ሺህ ዶላር ብድር፣ ለመንግስት ስራ የሚውል የ48 ሺህ ዶላር መኪና፣ እንዲሁም የ3 ሺህ 440 ዶላር ወርሃዊ የትራንስፖርትና የመኪና ጥገና ወጪ አበል እንደሚገኙበት ዘገባው ዘርዝሯል፡፡


Read 2847 times