Saturday, 22 July 2017 15:47

በጣይቱ የባህልና የትምህርት ማዕከል ዓመታዊ የኪነ ጥበብ ምሽት ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በአርቲስት ዓለምፀሐይ ወዳጆና በሙያ ባልደረቦቿ የሚመራውና መቀመጫውን አሜሪካ ያደረገው ዓመታዊ የኪነ ጥበብ ምሽት የፊታችን ሐሙስ ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ በአክሱም ሆቴል ይካሄዳል፡፡
በዕለቱ የተለያዩ ግጥሞችች፣ ወጎች፣ መነባንብ፣ በአርቲስት ታምሩ ንጉሴ የሚቀርብ የክራር ሙዚቃና ሌሎችም የኪነ ጥበብ ድግሶች ይቀርባሉ፡፡
የኢትዮጵያን ኪነ ጥበብ ለማሳደግና ለወጣት የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች መድረክ ለመፍጠር ታልሞ በየዓመቱ በሚዘጋጀው በዚህ ምሽት ላይ ምልዕቲ ኪሮስ፣ ወሰን ሰገድ ገ/ኪዳን፣ በላይ በቀለ ወያ፣ ሰለሞን ሞገስና ሌሎችም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ የተባለ ሲሆን በአገራችን የቅኔ ባህል ዙሪያ ባለ ቅኔው ዶ/ር ታደለ ገድሌ የቅኔ ዲስኩር ያቀርባሉም ተብሏል፡፡
በዕለቱ የኪነ ጥበብ አፍቃሪ በነፃ ምሽቱን እንዲታደም ግብዣ ቀርቧል፡፡

Read 731 times