Print this page
Saturday, 05 August 2017 11:57

በበገና እና በመዝሙራት ላይ የፓናል ውይይት ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማህበረ ቅዱሳን ስር የሚገኘው የአቡነ ጎርጎሪዎስ ስልጠና ማዕከል፣በበገና እና በመዝሙራት ዙሪያ በጥናታዊ ፅሁፎች ላይ የተመሰረተ የፓናል ውይይት፣ ዛሬ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በአምስት ኪሎ የማህበረ ቅዱሳን ህንፃ 3ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው አዳራሽ ያካሂዳል፡፡ ጥናታዊ ፅሁፎቹ፤ በመጥፋት ላይ ባሉት የበገናና የመዝሙራት ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ ሲሆን ከጥናታዊ ፅሁፎቹ በኋላ ሰፊ የፓናል ውይይት ይካሄዳል ተብሏል፡፡ በውይይቱ ላይ ሊቃውንት አባቶች፣ ባለድርሻ አካላትና የቀድሞ የአቡነ ጎርጎሪዎስ የዜማ መሳሪያዎችና የልሳነ ግዕዝ ተመራቂዎች ይሳተፋሉም ተብሏል፡፡

Read 1206 times
Administrator

Latest from Administrator