በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማህበረ ቅዱሳን ስር የሚገኘው የአቡነ ጎርጎሪዎስ ስልጠና ማዕከል፣በበገና እና በመዝሙራት ዙሪያ በጥናታዊ ፅሁፎች ላይ የተመሰረተ የፓናል ውይይት፣ ዛሬ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በአምስት ኪሎ የማህበረ ቅዱሳን ህንፃ 3ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው አዳራሽ ያካሂዳል፡፡ ጥናታዊ ፅሁፎቹ፤ በመጥፋት ላይ ባሉት የበገናና የመዝሙራት ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ ሲሆን ከጥናታዊ ፅሁፎቹ በኋላ ሰፊ የፓናል ውይይት ይካሄዳል ተብሏል፡፡ በውይይቱ ላይ ሊቃውንት አባቶች፣ ባለድርሻ አካላትና የቀድሞ የአቡነ ጎርጎሪዎስ የዜማ መሳሪያዎችና የልሳነ ግዕዝ ተመራቂዎች ይሳተፋሉም ተብሏል፡፡