Sunday, 06 August 2017 00:00

“የተገለጡ ዓይኖች” የግጥም መፅሐፍ ገበያ ላይ ዋለ

Written by 
Rate this item
(10 votes)

 የገጣሚ ሰለሞን ሞገስ (ፋሲል) አራተኛ ስራ የሆነው “የተገለጡ አይኖች” የግጥም መፅሐፍ ሰሞኑን ገበያ ላይ ዋለ፡፡ ከ75 በላይ በማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ስነ ልቦናዊ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ ግጥሞችን ያካተተው የግጥም መፅሐፉ፤ እጥር ምጥን ብሎ በ90 ገፆች የተቀነበበ ሲሆን በ40 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡መፅሀፉ በ3ኛው “ንባብ ለህይወት” የመፃህፍት አውደርዕይ ላይ ለምረቃ ከበቁ 28 መፃህፍት መካከል አንዱ ነበር፡፡ ገጣሚ ሰለሞን ሞገስ ከዚህ ቀደም “እውነትን ሰቀሏት”፣ “ከፀሀይ በታች” እና “ፅሞናና ጩኸት” የተሰኙ የግጥም መድበሎች ለንባብ ማብቃቱ ይታወሳል፡፡

Read 4194 times