የገጣሚ ሰለሞን ሞገስ (ፋሲል) አራተኛ ስራ የሆነው “የተገለጡ አይኖች” የግጥም መፅሐፍ ሰሞኑን ገበያ ላይ ዋለ፡፡ ከ75 በላይ በማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ስነ ልቦናዊ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ ግጥሞችን ያካተተው የግጥም መፅሐፉ፤ እጥር ምጥን ብሎ በ90 ገፆች የተቀነበበ ሲሆን በ40 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡መፅሀፉ በ3ኛው “ንባብ ለህይወት” የመፃህፍት አውደርዕይ ላይ ለምረቃ ከበቁ 28 መፃህፍት መካከል አንዱ ነበር፡፡ ገጣሚ ሰለሞን ሞገስ ከዚህ ቀደም “እውነትን ሰቀሏት”፣ “ከፀሀይ በታች” እና “ፅሞናና ጩኸት” የተሰኙ የግጥም መድበሎች ለንባብ ማብቃቱ ይታወሳል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና