Tuesday, 08 August 2017 00:00

“አርግዞ” የተወለደው ህንዳዊ ጨቅላ፣ አለምን አስደንቋል

Written by 
Rate this item
(3 votes)

   በአለማችን 200 ጨቅላዎች፣ የመንታቸውን ጽንስ አርግዘው ተወልደዋል

      ነገሩ በሳይንስ ፊክሽን ፊልም አልያም በልቦለድ ካልሆነ በገሃዱ አለም የሚከሰት ነው ብሎ ለማመን ቢያዳግትም፤ የእንግሊዙ ሚረር ግን በእርግጥም የሆነ ነው ይለዋል - ከሰሞኑ በህንድ የተከሰተውን አስደንጋጭ ክስተት፡፡
ዘገባው እንዳለው፤ የመውለጃ ቀኗ ሲቃረብ ከፍተኛ የህመም ስሜት የተሰማትና ለቅድመ ወሊድ ምርመራ ወደ አንድ ሃኪም ቤት ያመራችው የ19 አመቷ ህንዳዊት፤ መንታ ወንድሙን ያረገዘ ጨቅላ በቀዶ ህክምና ተገላግላለች፡፡
ጨቅላው 7 ሴንቲ ሜትር ያለውና ሙሉ የራስ ቅል፣ እጆች እና እግሮች ያሉትን መንታ ወንድሙን አርግዞ መወለዱን የጠቆመው ዘገባው፤ በተደረገለት ቀዶ ህክምና ጽንሱ እንደወጣለትና እሱም ሆነ እናቱ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙ አመልክቷል፡፡
በመላው አለም እስካሁን ድረስ 200 ያህል ተመሳሳይ ክስተቶች መፈጠራቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ ይህ ክስተት ከአምስት ሚሊዮን ወሊዶች በአንዱ ብቻ የመከሰት እድል እንዳለው ሃኪሞች መናገራቸውን አስረድቷል፡፡

Read 4069 times Last modified on Saturday, 05 August 2017 12:27