Wednesday, 09 August 2017 00:00

ጆርጅ ክሉኒ፣ 3ሺህ ሶርያውያን ስደተኛ ህጻናትን ሊያስተምር ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

   ታዋቂው የሆሊውድ የፊልም ተዋናይ ጆርጅ ክሉኒ እና ባለቤቱ አማል ክሉኒ በሊባኖስ የሚገኙ 3ሺህ ሶርያውያን ሰደተኛ ህጻናትን ሙሉ ወጪ በመሸፈን ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ የሚያስችል የበጎ ምግባር ፕሮጀክት ተግባራዊ ሊያደርጉ ነው ሲል አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
ጆርጅ ክሉኒና ባለቤቱ በጋራ ባቋቋሙት ፋውንዴሽን፣ ከጎግል ኩባንያ ጋር በፈጸሙት የጋራ ስምምነት፣ ሶርያውያኑን ስደተኛ ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት ለማስገባት፣ ከ2.25 ሚሊዮን ዶላር በላይ በጀት በመመደብ እቅዳቸውን እውን ለማድረግ እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ ዘገባው አመልክቷል፡፡ የስደተኞች ትምህርት ፕሮጀክቱ፣ ህጻናቱ በሰባት ትምህርት ቤቶች ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑም ተነግሯል፡፡
በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ የአገሪቱ ስደተኛ ህጸናት ከትምህርት ገበታቸው ውጭ መሆናቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ በሊባኖስ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሶርያውያን ስደተኞች እንደሚኖሩና ከእነዚህም መካከል 500 ሺህ ያህሉ ህጻናት እንደሆኑም አመልክቷል፡፡

Read 2015 times