በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ፤ ከአዲስ አበባ ጅግጅጋ ባለው መስመር፣ በሃረር እና በባቢሌ ከተሞች አካፋይ ላይ በመሳሪያ የታገዘ ግጭት መኖሩን በመጠቆም፣ ዜጎቹ ወደ አካባቢዎቹ እንዳይንቀሳቀሱ ትናንት አስጠንቅቋል፡፡ ኤምባሲው ባወጣው መግለጫ፣ በአካባቢዎቹ የተከሰተውን ግጭት ተከትሎም መንገዱ በፀጥታ ኃይሎች መዘጋቱንና የመከላከያ ሰራዊትም ወደ ስፍራው ማምራቱን አስታውቋል፡፡ የአሜሪካ ዜጎች በሥፍራው ከተገኙም እንቅስቃሴያቸው ጥንቃቄ የተሞላበት እንዲሆንና ግርግር ከበዛበት አካባቢ እንዲርቁም ኤምባሲው አሳስቧል፡፡
ባለፈው ዓመትና ዘንድሮ በከፊል፣ የአሜሪካ መንግስት በኦሮሚያና በአማራ ክልል የተፈጠሩ አለመረጋጋቶችን ተከትሎ፣ በተደጋጋሚ ተመሳሳይ የጉዞ ማስጠንቀቂያዎችን ለዜጎቹ ሲያስተላልፍ እንደነበር ይታወሳል፡፡
Published in
ዜና