የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ2009 በጀት ዓመት ካደረጋቸው አጠቃላይ እንቅስቃሴዎች 31.9 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱንና ከታክስ በፊት 14.6 ቢሊዮን ብር ማትረፉን አስታወቀ፡፡
ባንኩ በላከው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተገለፀው፤ በዓመቱ በተለያዩ ዘርፎች ባደረጋቸው እንቅስቃሴዎች ከወጪ ንግድ፣ ከሃዋላ፣ ከወጪ ምንዛሪ ግዥና ሌሎች አገልግሎቶች 4.5 ቢሊዮን ዶላር ማግኘቱንም አስታውቋል፡፡ ባንኩ ከብድር ተመላሽ መሰብሰብ የቻለው 64.6 ቢሊዮን ብር ሲሆን 94.5 ቢሊዮን ብር ለልዩ ልዩ የሥራ መስኮች አዲስ ብድር መሰጠቱን ገልጿል፡፡
ህብረተሰቡ ስለቁጠባ የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖረው ለማድረግ በሽልማት ላይ የተመረኮዘ ቁጠባን የማበረታታት ሥራ መሠራቱም ተገልጿል፡፡ በእነዚህ ተግባራት አማካኝነትም 76.4 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ ተቀማጭ ገንዘብ ማሰባሰብ መቻሉን መረጃው አመላክቷል፡፡ ይህ ክንውን የባንኩን ጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘብ በ2008 ከነበረበት 288.4 ቢሊዮን ወደ 364.9 ቢሊዮን ብር ማድረስ አስችሏል ተብሏል፡፡
የባንኩ ጠቅላላ ሀብት 485.7 ቢሊዮን ብር መድረሱንና የባንኩ ካፒታል ወደ 40 ቢሊዮን ብር ማደጉ ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአሁኑ ወቅት 1222 ቅርንጫፎች መድረሱንና፣ ሂሳብ ያላቸው የባንኩ ጠቅላላ ደንበኞች ቁጥርም 15.9 ቢሊዮን መድረሱን መግለጫው አመልክቷል፡፡
Saturday, 12 August 2017 00:00
ንግድ ባንክ በበጀት ዓመቱ 31.9 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ
Written by Administrator
Published in
ዜና
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል