Monday, 21 August 2017 00:00

የእንዳለ ጌታ ከበደ “ያልተቀበልናቸው” መፅሐፍ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

  የእውቁ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ “ያልተቀበልናቸው” የተሰኘ መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ መፅሐፉ ከ20 በላይ መጣጥፎችን፣ ወጎችን እና “የካሳ ፈረሶች” የተሰኘ ታሪካዊ የተውኔት ድርሰትን ያካተተ ሲሆን የዚህ መፅሐፍ አብይ ትኩረትም ባልህ፣ ታሪክ ሚዲያና ፖለቲካ መሆኑን ለመገንዘብ ተችሏል “ያልተቀበልናቸው” መፅሐፍ ከተጠቀሱት ታሪኮች በተጨማሪ ከኢትዮጵያና ከኤርትራ የተወለዱ ግለሰቦች በዚህ ዘመን ስለሚደርስባቸው ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጫና፣ በህክምና ሰበብ ስለሚፈጠሩ ሳንካዎች፣ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት በኢትዮጵያ ስለገጠመውና እየገጠመው ስላለው ተግዳሮት የሚያትት ነው ተብሏል፡፡
መፅሐፉ በ260 ገፆች ተቀንብቦ በ75 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ ደራሲው ከዚህ ቀደም “እምቢታ” ፣ ማዕቀብ፣ ኬርሻዶ፣ በዓሉ ግርማ ህይወቱና ስራዎቹ፣ ዛጎል፣ ደርሶመልስ የተሰኙ መፅሐፎች ለንባብ ያበቃ ሲሆን ከጥቁር ሰማይ ስር፣ የመኝታ ቤት ምስጢሮች እና ፅላሎት በተሰኘ አጫጭር ትረካዎቹ ይታወቃል፡፡

Read 3671 times