Saturday, 19 August 2017 13:10

ኢማ ስቶን በአመቱ ከፍተኛውን ገቢ ያገኘች የፊልም ተዋናይት ሆናለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   በ12 ወራት 26 ሚሊዮን ዶላር አግኝታለች

       በርካታ ታላላቅ ሽልማቶችን ባገኘው ላላ ላንድ ፊልም ላይ በመሪ ተዋናይነት የሰራቺው የሆሊውድ የፊልም ተዋናይት ኢማ ስቶን፣ ባለፉት 12 ወራት በድምሩ 26 ሚሊዮን ዶላር በማግኘት የአመቱ የአለማችን ከፍተኛ ተከፋይ የፊልም ተዋናይት ሆናለች፡፡
ፎርብስ መጽሄት ሰሞኑን ባወጣው ዘገባ እንዳለው፣ የ28 አመቷ የፊልም ተዋናይት ኢማ ስቶን ገቢ አምና ከነበረው 10 ሚሊዮን ዶላር የ160 በመቶ ጭማሪ በማሳየት 26 ሚሊዮን ዶላር የደረሰ ሲሆን፣ ለገቢዋ መጨመር ከፍተኛውን አስተዋጽኦ ያደረገላት አመቱን በስኬት እየገፋ ያለው ላላ ላንድ ፊልም ነው።
ታዋቂዋ የሂልም ተዋናይት ጀኔፈር አኒስተን በ25.5 ሚሊዮን ዶላር አመታዊ ገቢ ሁለተኛ ደረጃን የያዘች ሲሆን፣ አምና በአንደኛነት ተቀምጣ የነበረቺው ጄኔፈር ሎውረንስ ዘንድሮ በ24 ሚሊዮን ዶላር የሶስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን ፎርብስ መጽሄት አስታውቋል፡፡
ሜሊሳ ማካርቲኒ በ18 ሚሊዮን ዶላር፣ ሚላ ኩኒስ በ15.5 ሚሊዮን ዶላር የአራተኛና የአምስተኛ ደረጃን እንደያዙ የጠቆመው ፎርብስ፣ የዘንድሮዎቹ ምርጥ 10 ከፍተኛ ተከፋይ ሴት የፊልም ተዋንያን፣ ባለፉት 12 ወራት በድምሩ 172.5 ሚሊዮን ዶላር ያህል ገቢ ማግኘታቸው ተነግሯል፡፡

Read 956 times