Saturday, 26 August 2017 12:01

5 ደቡብ አፍሪካውያን በ“ሰውበላነት” ተጠርጥረው ታሰሩ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  አንድ ደቡብ አፍሪካዊ፣ የሰው ስጋ መብላት ሰለቸኝ ሲል ለፖሊስ እጁን መስጠቱን ተከትሎ፣ በ”ሰው በላነት” ተሳትፈዋል የተባሉ 5 ሌሎች ተጠርጣሪዎች በፖሊስ  ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ዘ ኢንዲፔንደንት ከትናንት በስቲያ ዘግቧል፡፡
ግለሰቡ ለረጅም ጊዜ የሰዎችን ስጋ በመብላት እንደቆየ ባለፈው ረቡዕ ለፖሊስ የተናዘዘ ሲሆን ደብቆት የነበረውን ቁራጭ የሰው እጅና እግርም ለፖሊስ አስረክቧል ተብሏል፡፡ ፖሊስ የግለሰቡን ጥቆማ መሰረት በማድረግ፣ ክዋዙሉ ናታል በተባለው የአገሪቱ ግዛት ባደረገው ፍተሻ፣ በርካታ የሰው አካላት ቁርጥራጮችን ማግኘቱን ዘገባው ገልጧል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ሰው በመግደል፣ በመቆራረጥና የሰውነት ክፍሎችን በቤት ውስጥ በመደበቅ ክስ እንደሚመሰረትባቸው የጠቆመው ዘገባው፤ በአገሪቱ አንዳንድ ማህበረሰቦች ዘንድ የሰው ስጋ መብላት፣ ከእርኩስ መንፈስና ከበሽታ ይፈውሳል የሚል አጉል እምነት እንዳለ አመልክቷል፡፡

Read 1475 times