Saturday, 26 August 2017 12:13

ብሪጅስቶን ‹‹ባንዳግ›› የተሰኘ አዲስ አገልግሎት ጀመረ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

• 400 የብሪጅስቶን ጎማ የገዛ፣ ታይላንድን ለ1ሳምንት በነጻ ይጎበኛል
       • 1ሺ ጎማ ለሚገዙ፣ የ160ሺ ብር ቅናሽ ይደረግላቸዋል

     በኢትዮጵያ  የታዋቂው ብሪጅስቶን ጎማ ብቸኛ አከፋፋይ  ካቤ ኃ. የተ. የግል ማህበር፣ “ባንዳግ” የተሰኘ አዲስ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አስታወቀ፡፡  ከጃፓኑ ብሪጅስቶን አለም አቀፍ ኩባንያ የመጡ ኃላፊዎችና የካቤ  አመራሮች፣ ከትላንት በስቲያ ሐሙስ በሸራተን አዲስ፣ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ “ባንዳግ” ለአገራችን እንግዳ ቢሆንም  በመላው አለም ለረጅም አመታት በእጅጉ የሚታወቅ አገልግሎት መሆኑን ጠቁመው፣ ይህ አዲስ አገልግሎት፣ የሥራ ጊዜው ያበቃለት ጎማን እንደ አዲስ ለመጠቀም የሚያስችል ነው  ብለዋል፡፡
የብሪጅስቶን አመራሮች እንደገለፁት፤ የ”ባንዳግ”ን አገልግሎት ኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመር ከፍተኛ በጀት የተመደበለት  ሲሆን አገልግሎቱም ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው ነው ተብሏል፡፡ ከአገልግሎት ውጭ የሆነን አሮጌ ጎማ፣ በብሪጅስቶን “ባንዳግ” አገልግሎት በማሳደስ፣ የጎማ ግዢ ወጪን በ50 ፐርሰንት መቀነስ እንደሚቻል የጠቆሙት አመራሮቹ፤ አገልግሎቱ የሚሰጠው  ዘመኑ ባፈራው የረቀቀ ቴክኖሎጂ በመሆኑ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና አስተማማኝ ነው ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል፤ ብሪጅስቶን፣ ለደንበኞቹ አዲስ የሽያጭ ማስተዋወቂያ ስጦታ ማዘጋጀቱን ሰሞኑን አብስሯል፡፡ በዚህም መሰረት፣ 400 የብሪጅስቶን ጎማ ለሚገዙ ደንበኞች፤ ለአንድ ሳምንት ሙሉ ወጪያቸውን ችሎ፣ ታይላንድን ያስጎበኛል፡፡  በተጨማሪም፣ 1ሺ ጎማ ለሚገዙ፣ የ160 ሺ ብር ቅናሽ የሚያደርግ ሲሆን 50 ጎማ ለሚገዙ ደግሞ  የ30ሺ ብር ቅናሽ እንደሚደረግላቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡ ይህ የሽያጭ ማስተዋወቂያ ስጦታ፣ ለ3 ወራት ብቻ የሚዘልቅ ሲሆን  በመጪው ህዳር ወር አጋማሽ ላይ (ኖቬምበር 30 ቀን 2017) የሚያበቃ ይሆናል ተብሏል፡፡

Read 2646 times