Print this page
Sunday, 03 September 2017 00:00

ስውሩና ያልተነገረው የአይሁዳውያንና የኢትዮጵያን ታሪክ የተሰኘ መፅሀፍ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(5 votes)

   የዕውቁ የታሪክ ተመራማሪና የስነ-ፅሁፍ ባለሙያ ፕሬፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ፣ “ስውሩና ያልተነገረው የአይሁዳውያንና ኢትዮጵያውያን ታሪክ” የተሰኘ መፅሀፍ፣ ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡
መፅሀፉ በዋናነት፣ የሁለቱ አገራት ህዝቦች ከ4 ሺ ዓመታት በላይ ስላላቸው ትስስር፤ ስለ ዮዲት ጉዲት ያልተነገሩና ለኢትዮጵያ ስላደረገቻቸው መልካም ተግባራት፤ ስለ አፋር ህዝብና በስሙ ስለተሰየመው አፍሪቃና በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ትንታኔ ይሰጣል፤ ተብሏል፡፡
ፕሮፌሰር ፍቅሬ ከዚህ ቀደም ይህንን መፅሀፍ “The hidden and untold history of the Jewish people and Ethiopian” በሚል ርዕስ በእንግሊዝኛ ፅፈው አቅርበውት እንደነበር ተገልጿል። መፅሀፉ በ238 ገፅ ተቀንብቦ፣ በ101 ብር ከ20 ሳንቲም ለገበያ ቀርቧል። ፕሮፌሰር ፍቅሬ በቅርቡ ለንባብ ካበቁት፣‹‹የኦሮሞና የአማራ እውነተኛ የዘር ምንጭ” ከተሰኘው አነጋጋሪ መፅሀፋቸው በተጨማሪ፣ በእንግሊዝኛ፣ በጀርመንኛና በአማርኛ በርካታ ግጥሞችን፣ ተውኔቶችንና ከ60 በላይ አጫጭር መጣጥፎችን ለንባብ ማብቃታቸው ይታወሳል፡፡


Read 7123 times
Administrator

Latest from Administrator