Print this page
Monday, 11 September 2017 00:00

ብርሃንና ሰላም፤ የስማርት ካርድ ህትመት ሊጀምር ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  አንጋፋው ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት፤ ከጀርመኑ ሙልባወር ኩባንያ ጋር በመተባበር የስማርት ካርድ ህትመት ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ፡፡
ማተሚያ ቤቱ ከዚህ ቀደም ሚስጥራዊ ህትመቶችን በወረቀትና በቀለም ቴክኖሎጂ ያከናውን እንደነበር የጠቆሙት የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ተካ አባዲ፤ በዓለማቀፍ ደረጃ በአብዛኛው ሚስጥራዊ ህትመቶች ወደ ዲጂታል ቴክኖሎጂ እየተሸጋገሩ በመሆኑ፣ ማተሚያ ድርጅቱ ራሱን ለማዘመን ቴክኖሎጂውን ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት፣ የስማርት ካርድ ምርቶችን ለመጀመር ማቀዱን አስታውቀዋል፡፡
በዚህ ቴክኖሎጂ በመታገዝ በከፍተኛ የውጪ ምንዛሬ በውጪ ሀገራት በስማርት ካርድ ቴክኖሎጂ የሚታተሙ የባንክ ገንዘብ ማውጫ ካርዶች፣ ሲም ካርዶች፣ የመታወቂያ ካርድ፣ ፓስፖርት የመሳሰሉትን በሀገር ቤት ለማተም ያስችላል ተብሏል፡፡
የማተሚያ ቤቱ አመታዊ ትርፍ ከነበረበት 8 ሚ. ወደ 1.5 ቢሊዮን ብር ማደጉንና ትርፋማ መሆኑን ያወሱት ስራ አስኪያጁ፤ ቴክኖሎጂውን በስራ ላይ ለማዋል የገንዘብ አቅም ችግር የለብንም ብለዋል፡፡ ቴክኖሎጂውን ለመተግበር ከ125 እስከ 150 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ በመጠቆም፡፡ አገልግሎቱም ከ6-8 ወር ባለው ጊዜ ውስጥ እንደሚጀመር አቶ ተካ ተናግረዋል፡፡

Read 1833 times
Administrator

Latest from Administrator