Print this page
Monday, 11 September 2017 00:00

12 ተቃዋሚ ፓርቲዎች በጋራተወካዮች እንደሚደራደሩ አስታወቁ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

      ከኢህአዴግ ጋር በድርድር ላይ ከሚገኙ ተቃዋሚዎች መካከል መኢአድ እና ኢዴፓን ጨምሮ 12 ፓርቲዎች በጋራ ተወካዮች ለመደራደር
ተስማምተዋል፡፡ ፓርቲዎቹ ከትናንት በስቲያ በሰጡት መግለጫ፤ አንድ ዓይነት የመደራደሪያ አጀንዳዎችን በጋራ ቀርፀው ለአደራዳሪው አካል ማስገባታቸውን ጠቁመዋል፡፡ ለድርድሩ በጋራ ለመቅረብ የተስማሙት ፓርቲዎች፡- የመላው ኢትዮጵያውያን አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ የኢትዮጵያውያን ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ)፣ ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ፣ አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ፣ የአዲስ ትውልድ ፓርቲ (ኢትፓ)፣ የወለኔ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ድርጅት፣ የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ አንድነት ንቅናቄ (ኢድአን)፣ የመላ ኢትዮጵያውያን ብሔራዊ ንቅናቄ (መኢብን)፣ የመላ ኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (መኢዴፓ)፣መሆናቸው ታውቋል፡፡ ፓርቲዎቹን በተደራዳሪነት እንዲወክሉም የመኢአድ ም/ፕሬዚዳንት አቶ ሙሉጌታ አበበ፣ የኢዴፓ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጫኔ ከበደና የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ሊቀ መንበር አቶ ትዕግስቱ
አወሉ ተመርጠዋል፡፡ ድርድሩ ላይ የተበታተነ ሀሳብ ይዞ ከመቅረብ ይልቅ በአንድ አላማና አቋም ገዥውን ፓርቲ ለመገዳደር በማሰብ ፓርቲዎቹ በጋራ ለመቅረብ መወሠናቸውን አስታውቀዋል፡፡

Read 1275 times
Administrator

Latest from Administrator