Monday, 11 September 2017 00:00

9ኛው ዙር “ህብረትርኢት” የኪነ የጥበብ ምሽት አርብ ይካሄዳል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

 ማይና ፕሮሞሽንና ኢንተርቴይመንት ከኢትዮጵያ ሆቴል ጋር በመተባበር፣ ወር በገባ በመጀመሪያው አርብ ምሽት የሚያካሂዱት ዘጠነኛው ዙር “ህብረ ትርኢት” የኪነ-ጥበብ ምሽት የፊታችን አርብ ከ11፡00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ሆቴል ይቀርባል፡፡
 የአዲሱ ዓመት የመጀሪያው ዝግጅት በሆነው በዚህ ፕሮግራም ግጥም፣ ወግ፣ ስታንዳፕ ኮሚዲ፣ ሙዚቃና አጭር ተውኔት የሚቀርብ ሲሆን ፍላጎት ያለው በኪነ ጥበብ ምሽቱ ላይ እንዲታደም አዘጋጆቹ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

Read 1902 times