Print this page
Monday, 18 September 2017 10:43

ቬንዙዌላውያን ጥንቸል እንዲበሉ በመሪያቸው ቢመከሩም በጄ አላሉም

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  “አትቀልዱ ርሃብን የምናሸንፈው ጥንቸል እየበላን ነው” - የግብርና ሚ/ር

        አነጋጋሪው የቬንዙዌላ ፕሬዚዳንት ኒኮላስ ማሩዶ በቅርቡ የምግብ እጥረትን ለመቋቋም ጥንቸል እያረቡ እንዲበሉ ለዜጎቻቸው ያስተላለፉት ምክር ከባህልና እምነት ጋር በተያያዘ ተቃውሞ እንደገጠመው ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
በኢኮኖሚ ቀውስ በተመታችው ቬንዙዌላ፣ በተለይ ህጻናት በከፍተኛ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እየተጎዱ እንደሚገኙ የጠቆመው ዘገባው፤ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ማዱሮም በቅርቡ ባደረጉት ንግግር፣ ዜጎች በመኖሪያ ቤታቸው ጥንቸሎችን እያረቡ ቢመገቡ በቂ የእንስሳት ፕሮቲን ሊያገኙ እንደሚችሉ መምከራቸውንና ጉዳዩ ግን ተቀባይነት አለማግኘቱን አመልክቷል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ለአገሪቱ የግብርና ሚኒስቴር ባስተላለፉት መመሪያ፣ በተለያዩ 15 የአገሪቱ አካባቢዎች የጥንቸል እርባታ ፕሮጀክት መጀመሩንና ግልገል ጥንቸሎች ለእርባታ መከፋፈላቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ ይሄም ሆኖ ግን ነዋሪዎቹ ከሃይማኖታቸውና ከባህላቸው አንጻር የጥንቸል ስጋ ለመብላት ባለመፍቀዳቸው፣ጥንቸሎቹን አርብተው ለምግብነት ከማዋል ይልቅ ለቤት ማድመቂያነት እየተጠቀሙባቸው እንደሆነ ተረጋግጧል ብሏል፡፡
የአገሪቱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች፣ የፕሬዚዳንቱን የጥንቸል እቅድ “የጅል ቀልድ” በማለት ያጣጣሉት ሲሆን፣ የግብርና ሚኒስትሩ ፍሬዲ በርናል ግን “አትቀልዱ ርሃብን የምናሸንፈው ጥንቸል እየበላን ነው” ማለታቸውን ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 2175 times
Administrator

Latest from Administrator