ከዚህ በፊትም ፕሬዚዳንቱን በስልጣን ለማቆየት ህገ መንግስቱ ተሻሽሏል
በኡጋንዳ የገዢው ፓርቲን የሚወክሉ የፓርላማ አባላት፣ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት የዕድሜ ጣራ 75 አመት እንዲሆን የሚገድበውን የህገ መንግስት አንቀጽ እንዲሰረዝ የሚጠይቀውን የውሳኔ ሃሳብ ባለፈው ማክሰኞ በሙሉ ድምጽ መደገፋቸውን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
የፕሬዚዳንቱን የእድሜ ገደብ ለማስቀረት ያለመው የውሳኔ ሃሳቡ፣ የአገሪቱን ህገ መንግስት በማሻሻል፣ የ72 አመቱን ፕሬዚዳንት ዮሪ ሙሴቬኒ፣ በ2021 በሚካሄደው ቀጣዩ የአገሪቱ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ እንዲወዳደሩ ለማስቻል የተደረገ ሙከራ ነው ሲሉ ተቃዋሚዎች ትችት መሰንዘራቸውን ዘገባው ገልጧል፡፡
ፕሬዚዳንት ሙሴቬኒ በቀጣዩ ምርጫ ዕድሜያቸው ከ75 አመት በላይ ስለሚሆን፣ በህገ መንግስቱ መሰረት፣ ለፕሬዚዳንትነት መወዳደር እንደማይችሉ የጠቆመው ዘገባው፤ ፓርቲያቸው ናሽናል ሬዚዝታንስ ሙቭመንት ግን፣ ያለ አግባብ ህግ በማሻሻል በስልጣን እንዲቆዩ ለማድረግ ዘመቻ መጀመሩን አመልክቷል፡፡
ፕሬዚዳንቱ ከሁለት ወራት በፊት በጉዳዩ ላይ በሰጡት አስተያየት፣ አሁን የዕድሜ ገደብን በተመለከተ የምንወያይበት ጊዜ ላይ አይደለሁም፣ አገር በመምራቱ ላይ ነው ትኩረት የማደርገው ሲሉ መናገራቸውንም ዘገባው አስታውሷል፡፡
የዕድሜ ገደቡን የሚያነሳው የውሳኔ ሃሳብ በፓርላማው የሚጸድቅ ከሆነ፣ የፕሬዚዳንት ሙሴቬኒን ስልጣን ለማራዘም ሲባል 20 አመታትን ባስቆጠረው የአገሪቱ ህገ መንግስት ላይ የተደረገ ሁለተኛው ማሻሻያ እንደሚሆን የጠቆመው ዘገባው፤ በ2005 ላይም ሙሴቬኒን በስልጣን ላይ ለማቆየት ሲባል ከሁለት የስልጣን ዘመን በላይ መግዛትን የሚከለክለው የህገ መንግስቱ አንቀጽ መሻሻሉን አስታውሷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል