አዲስ አበባ የጤናና የቢዝነስ ኮሌጅ፣ ለ13ኛ ጊዜ በዲግሪና በደረጃ አራት ያሰለጠናቸውን 429 ተማሪዎች ባለፈው ሳምንት በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ አስመረቀ።ተመራቂዎቹ በነርሲንግ፣ በጤና መኮንን፣ በክሊኒካል ነርሲንግና በላብራቶሪ ቴክኒሺያን የትምህርት ዘርፍ
የሰለጠኑ እንደሆኑ ታውቋል፡፡ኮሌጁ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ድረስ በሶማሌ ላንድ ሀርጌሳ የሚገኘውን ካምፓስ ጨምሮ
በአዲስ አበባና በተለያዩ ክልሎች ባሉት ካምፓሶቹ፣ከ47ሺህ በላይ የህክምና ባለሙያዎችን አሰልጥኖ በማስመረቅ በጤናው ዘርፍ ያለውን የባለሙያ ክፍተት ሲሞላ መቆየቱን የኮሌጁ ባለቤትና ፕሬዚዳንት ተናግረዋል፡፡ ከተመረቁ 47 ሺህ ባለሙያዎች መካከል
ከ10 ሺህ በላይ የሚሆኑት በኮሌጁ ነፃ የትምህርት እድል ተጠቃሚዎች እንደነበሩ ያስታወሱት ፕሬዚዳንቱ፤
በየካምፓሶቹ በዓመት ለ20 ተማሪዎች ነፃ የትምህርት እድል እንደሚሰጥና በተለይ መክፈል ባለመቻል መማር ላልቻሉ ሴት ልጆች ቅድሚያ በመስጠት ኃላፊነቱን ሲወጣ እንደቆዩ አክለው ገልፀዋል፡፡ተማሪዎች እዚህ ትምህርታቸውን አጠናቅቀው ለከፍተኛ ትምህርት አሜሪካ በሚሄዱበት ወቅት ተቀባይነት የሚያስገኝ፣ በአሜሪካ እውቅና ያለው ብቸኛ ኢትዮጵያዊ ኮሌጅ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ በምርቃቱ ዕለት አስታውቀዋል
Published in
ንግድና ኢኮኖሚ