Saturday, 30 September 2017 14:45

አስተራዜንካ በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች ነፃ የደም ግፊት ምርመራዎች አካሄደ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

አስትራዜንካ  በመላው ዓለም የሚከበረውን ‹‹የዓለም የልብ ቀን›› ምክንያት በማድረግ ነፃ የደም ግፊት ምርመራዎች እና የምክር ድጋፎችን በትናንትናው እለት በአዲስ አበባ እና በሌሎች የክልል ከተሞች አከናወነ፡፡
‹‹ሄልዚ ሃርት  አፍሪካ” በተሰኘው ፕሮግራሙ   አስትራዜንካ ነፃ የደም ግፊት ምርመራዎች እና የምክር ድጋፎችን  ያከናወነው በአዲስ አበባ ከተማ በሜክሲኮ፤ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል፣ በሾላ ገበያ እና ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን አካባቢ በሚገኙ አውራ ጎዳናዎች አደባባዮች እንዲሁም በክልሎች በጅማ፣ ሃዋሳ፣ ሆሳዕና ፤መቀሌ፣ ሃረር እና ድሬደዋ ከተሞች  በመሰማራት ነው፡፡ የዓለም ልብ ቀን ከ2012 እኤአ ጀምሮ በመላው ዓለም በተለያዩ ዘመቻዎች ሲከናወን የቆየ ሲሆን ከልብ ህመም ጋር በተያያዘ የሚከሰተውን የሞት አደጋ እስከ 2025 እኤአ በ25 በመቶ ለመቀነስ በተያዘ ዓላማ ዘንደሮ ተከብሯል፡፡ አስትራዜንካ የደም ግፊት ምርመራዎች በማከናወን የልብ ጤናን ለመጠበቅ  መደረግ ስለሚችሉ ቅድመ ጥንቃቄዎች ግንዛቤ ለመፍጠር ተንቀሳቅሷል፡፡  
“በደም ግፊት ማንም ሰው መሞት የለበትም” በሚል መርህ የሚንቀሳቀሰው አስትራዜንካ ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ የጤና ጥበቃ ሚኒስተር ጋር በአጋርነት ለመስራት ስምምነት ያደረገው  ከዓመት በፊት ሲሆን፤ በሔልዚ ሃርት አፍሪካ ፕሮግራሙ የደም ግፊት በሽታን ለመዋጋት የሚደረገውን እንቅስቃሴ ማገዝ እንዲሁም በሽታውን ለመከላከል የሚያስችሉ የአሰራር መዋቅሮችን ከአገሪቱ የጤና አስተዳደር ጋር አጣጥሞ ለማከናወን ድጋፍ በመስጠት ኢትዮጵያውያን የነፃ ደም ግፊት ምርመራዎች እና የምክር አገልግሎቶችን እንዲያገኙ  እየተንቀሳቀሰ ነው፡፡
አስትራዜንካ  ባለፈው 1 ዓመት ለ900 የጤና ባለሙያዎች እና የህክምና ድጋፍ ሰጪዎች ስልጠና የሰጠ ሲሆን በሰባት የአገሪቱ ክልሎች በሚገኙ 12 ሆስፒታሎች እና 36 የጤና ማዕከላት የተቀናጀ የአሰራር መዋቅርን ዘርግቷል፡፡ የህክምና ተቋሙ ባለፈው 1 ዓመት ነፃ የደም ግፊት ምርመራዎችን ከ200ሺ በላይ ለሚገመቱ ኢትዮጵያውያን ያከናወነ ሲሆን ፤ በሄልዚ ሃርት አፍሪካ ፕሮግራሙ ከደም ግፊት ጋር በተያያዘ ደረጃውን የጠበቀ ህክምና፤ እንክብካቤ እና የተሟላ አገልግሎት የሚሰጥበትን ሁኔታ በመላው ኢትዮጵያ ለማስፋፋት በትኩረት እየሰራ ቆይቷል፡፡






Read 1475 times