Saturday, 30 September 2017 15:11

የአሜሪካና ሰ/ ኮርያ ዛቻ፣ እነ ዙክበርግን በቀን፣ 16 ቢ. ዶላር አክስሯል

Written by 
Rate this item
(3 votes)

የፌስቡኩ መስራች ማርክ ዙክበርግ፣ የአማዞኑ ባለቤት ጄፍ ቤዞስ እና የቻይናው አሊባባ ኩባንያ መስራች ጃክ ማ ከሰሞኑ ተጧጡፎ በቀጠለውየአሜሪካና የሰሜን የቃላት ጦርነት ሳቢያ በአንድ ቀን ውስጥ በድምሩ 16 ቢሊዮን ዶላር ያህል እንዳጡ ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግቧል፡፡በሁለቱ አገራት መሪዎች መካከል የቃላት ጦርነቱ መጧጧፉንና የሰሜን ኮርያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አገራቸው በአሜሪካ ላይ ጥቃትእንደምትሰነዝር ማስታወቃቸውን ተከትሎ፣የአለማቀፍ ኢንቨስተሮች የግጭት ስጋት ማየሉንና ብዛት ያለው አክሲዮናቸውን መሸጣቸውንየጠቆመው ዘገባው፤በዚህም ሳቢያ ባለፈው ሰኞ በዓለማቀፍ የአክስዮን ገበያዎች ላይ ከፍተኛ የዋጋ ቅናሽ መታየቱን አመልክቷል፡፡በዕለቱ የፌስቡኩ መስራች ማርክ ዙክበርግ፣የኩባንያው የተጣራ ሃብት በ3.2 ቢሊዮን ዶላር እንደቀነሰበት የጠቆመው ዘገባው፤የአሊባባውባለቤት ጃክ ማ፤ 1.3 ቢሊዮን ዶላር፣ የአማዞኑ ጄፍ ቤዞስ፤ 1.2 ቢሊዮን ዶላር በተመሳሳይ ሁኔታ መክሰራቸውንም አስረድቷል፡፡

Read 2195 times