Saturday, 07 October 2017 15:04

“ስምንተኛው አዲስ ሚዩዚክ አዋርድ” በቅርቡ ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በህዝብ የተመረጡ የኪነጥበብ ሥራዎች ይሸለማሉ

      በዛሚ 90.7 ኤፍኤም፣ በ2001 ዓ.ም የተጀመረውና በህዝብ ምርጥ የተባሉ የኪነጥበብ ሥራዎችንና ሙያተኞችን በየዓመቱ የሚሸልመው “8ኛው አዲስ ሚዩዚክ አዋርድ” ጥቅምት 6 ቀን 2010 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ በሐርመኒ ሆቴል ይካሄዳል፡ ፡ በስምንት ዘርፎች የኪነ ጥበብ ሥራዎችን በህዝብ ምርጫ አወዳድሮ አሸናፊዎችን የሚሸልመው “አዲስ ሚዩዚክ አዋርድ”፤ የዘንድሮውን ለየት የሚያደርገው በጄቲቪ ኢትዮጵያም መጀመሩ እንደሆነ የፕሮግራሙ አዘጋጅ ይገረም ስንታየሁ (ዲጄ ቤቢ) ገልጿል፡፡ሽልማቱም “የዓመቱ ምርጥ አልበም”፣ “ምርጥ ነጠላ
ዜማ”፣ “ምርጥ የሙዚቃ ቪዲዮ”፣ “ምርጥ አዲስ ድምፃዊ”፣ “ምርጥ የሙዚቃ አቀናባሪ”፣ “ምርጥ ፊልም”፣ “ምርጥ ተዋናይ” እና “ምርጥ ተዋናይት”
በሚሉ ስምንት ዘርፎች አሸናፊዎችን የሚሸልም ሲሆን “የኪነ ጥበብ ባለውለታ” በሚል ልዩ ተሸላሚ እንደሚኖርም የሽልማቱ አዘጋጅ ዲጄ ቤቢ ጨምሮ ገልጿል፡፡በእለቱ ሁለት ትልልቅ የሙዚቃ ባንዶች ከታዋቂ ድምፃውያን ጋር የሙዚቃ ስራቸውን እንደሚያቀርቡ የጠቆመው ዲጄ ቤቢ፤ በፕሮግራሙ ላይ መታደም የሚቻለው በግብዣ ካርድ እንጂ የመግቢያ ትኬት እንደማይሸጥ በመጠቆም፣ ሰዎች ተጭበርብረው እንዳይገዙም አሳስቧል፡፡

Read 2506 times