ኢቴል አድቨርታይዚንግና ኮሙኒኬሽን ከቱርኩ መንግስታዊ ድርጅት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው “8ኛው አዲስ ቢዩልድ ዓለም አቀፍ የኮንስትራክሽን የንግድ ትርዒት” ትናንት በሚሊኒየም አዳራሽ የተከፈተ ሲሆን እስከ ሰኞ እንደሚቆይ ታውቋል፡፡
የአዘጋጅ ድርጅቱ ዋና ሥራ አሥኪያጅ ወ/ሮ ሃይማኖት ተስፋዬ ባለፈው ማክሰኞ በጎልደን ቱሊፕ ሆቴል ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ “የኮንስትራክሽን መሳሪያዎችና ቴክኖሎጂዎች” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው የንግድ ትርዒት ዓላማ፤ የኮንስትራክሽን መሳሪያዎችና
ቴክኖሎጂዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ የደረሱበትን ደረጃ በዘርፉ ለተሰማሩ የአገር ውስጥ ኮንትራክተሮች በማስተዋወቅ፣ አምራችና ገዢን ማገናኘት ነው ብለዋል፡፡ በዚህ ኤግዚቢሽን ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ12 አገሮች ማለትም፣ ከቱርክ ከጀርመን፣ ከኢጣሊያ፣ ከቤልጂየም፣
ከቻይና፣ ከቱኒዚያ፣ ከሳዑዲ ዐረቢያ፣ ከተባበሩት ዐረብ ኢመሬትስ፣ ከቡልጋሪያና ከአሜሪካ የተውጣጡ 125 ድርጅቶች፣ አገሮቻቸው የደረሱበትን የመጨረሻ ቴክኖሎጂ እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል፡፡
Saturday, 14 October 2017 15:15
8ኛው አዲስ ዓለም አቀፍ የኮንስትራክሽን ንግድ ትርዒት እየተካሄደ ነው
Written by Administrator
Published in
ዜና