Saturday, 14 October 2017 15:35

ፎርብስ የላቀ ዕድገት ያስመዘገቡ የአለማችን ኩባንያዎችን ይፋ አደረገ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ታዋቂው ፎርብስ መጽሔት በአጠቃላይ ዕድገትና በትርፋማነት አለምን ይመራሉ ያላቸውን የ2017 ቀዳሚ ኩባንያዎች ዝርዝር ባለፈው ማክሰኞ ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ ዳማክ ፕሮፐርቲስ የተባለው የተባበሩት አረብ ኤሜሪትስ የሪልስቴት ኩባንያ የአንደኛነት ደረጃን ይዟል፡፡ፎርብስ የኩባንያዎችን የሽያጭ፣ የትርፍ፣ የሃብት መጠንና የገበያ ዋጋ መሰረት በማድረግ ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋ ባደረገው በዚህ የቀዳሚ ባለዕድገት ኩባንያዎች ደረጀ ዝርዝር 1ኛ ደረጃን የያዘውና በ2016 የ1.9 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ያገኘው ዳማክ ፕሮፐርቲስ፣ በመላው መካከለኛው ምስራቅ ሰፋፊየግንባታ ፕሮጀክቶችን እንደሚሰራ ተነግሯል።
መርሴድስ ቤንዝን ጨምሮ ከ50 በላይ የተለያዩ ውድ መኪኖችን በማከፋፈል የሚታወቀውና በ2016 28.03 ሚሊዮን መኪኖችን በመሸጥ ከፍተኛ ገቢ ያገኘው የቻይና ግዙፉ የመኪና አከፋፋይ፣ ቻይና ግራንድ አውቶሞቲቭ ሰርቪስስ፣ በፎርብስ ዝርዝር የ2ኛነት ደረጃን ይዟል፡፡በሪልስቴት ዘርፍ የተሰማሩት ግሪንላንድ ሆልዲንግስ እና ሜልኮ ኢንተርናሽናል የ3ኛ እና የ4ኛ ደረጃን ሲይዙ፣ ሸቀጣሸቀጦችን ለተጠቃሚዎች በማድረስ ዘርፍ የተሰማራው ኤስኤፍ ሆልዲንግስ የተባለ ኩባንያ በበኩሉ፣ 5ኛው የአለማችን ቀዳሚ የእድገት ገስጋሽ ኩባንያ ሆኗል፡፡ፎርብስ ከዚህ በተጨማሪም በዓመቱ እጅግ ከፍተኛ ከበሬታንና ታማኝነትን ያገኙ የዓለማችን ኩባንያዎች ደረጃ ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ 351 ሺህ ሰራተኞችን ቀጥሮ የሚያሰራውና በ2016 ዓ.ም የ90 ቢሊዮን ዶላር ሽያጭ አስመዝግቦ፣ 6.4 ቢሊዮን ዶላር ያተረፈው  የጀርመኑ ሲመንስ ኩባንያ

ቀዳሚነቱን ይዟል፡፡
የፈረንሳዩ የጎማ አምራች ሚሼሊን ግሩፕ እና አልፋቤት ጎግል ከፍተኛ ተአማኒነትን በማግኘት ከዓለማችን ኩባንያዎች ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን

መያዛቸውን የገለጸው ፎርብስ፤ የጃፓኑ ኒንቲዶ አራተኛ ደረጃ ላይ መቀመጡን ጠቁሟል፡፡

Read 1886 times