Saturday, 21 October 2017 13:05

ሞቅታ ሌላ ቋንቋን አቀላጥፎ ለመናገር ያስችላል ተባለ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

አንድ ሁለት ሲል፣ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ እንግሊዘኛ መቀላቀል የሚያበዛ ሰው ገጥሞዎት አያውቅም?
የዩኒቨርሲቲ ኦፍ ሊቨርፑል ተመራማሪዎች ከሰሞኑ ይፋ ያደረጉት የጥናት ውጤት፣ እንደዚህ ያሉ ሰዎችን በተመለከተ አዲስ ነገር ይዞ መጥቷል ይላል የዴይሊ ሜይል ዘገባ፡፡ ዘገባው እንዳለው፣ የዩኒቨርሲቲው ተመራማሪዎች በኒዘርላንዱ ማስትሪችት ዩኒቨርሲቲ በሚማሩና አፋቸውን በጀርመንኛ ቋንቋ በፈቱ ተማሪዎች ላይ ባደረጉት ጥናት፤ተማሪዎቹ በደህናቸው ከሚናገሩት ይልቅ አንድ ሁለት አልኮል ተጎንጭተው የሚናገሩት ሁለተኛ ቋንቋቸው የሆነው የደች ቋንቋ ንግግራቸው የተሻለ፣ የተቀላጠፈና ያማረ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የዩኒቨርሲቲው መምህርና የጥናት ቡድኑ ባልደረባ የሆኑት ዶክተር ኢንግ ኬርስበር እንደሚሉት፤ አንድ ሰው አልኮል ወሰድሰድ ሲያደርግ ሁለተኛ ቋንቋውን የበለጠ አቀላጥፎ እንደሚናገር ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ይሁን እንጂ ይላሉ ዶክተሩ፤ ይሁን እንጂ ከሞቅታ አልፎ ጥንብዝ ብሎ የሰከረ ሰው ግን፣ በደህናው ከሚናገረው  የባሰ የተበላሸ ንግግር እንደሚያደርግም በጥናቱ ተረጋግጧል፡፡

Read 2639 times