Monday, 23 October 2017 00:00

በየቀኑ 15 ሺህ ህጻናት መከላከል በሚቻሉ በሽታዎች ይሞታሉ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 በአለማችን ተቅማጥንና ወባን በመሳሰሉ በቅድመ ጥንቃቄ ልንከላከላቸው በምንችላቸው በሽታዎች ሳቢያ በየቀኑ 15 ሺህ ያህል ህጻናት ለህልፈተ ህይወት እንደሚዳረጉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከትናንት በስቲያ ባወጣው ሪፖርት ይፋ አድርጓል፡፡
እድሜያቸው ከአምስት አመት በታች የሆኑ ህጻናትን በከፍተኛ ሁኔታ ለሞት እየዳረጉት ከሚገኙት መሰል በሽታዎች መካከል ኒሞኒያ፣ ተቅማጥና ወባ ቀዳሚውን ስፍራ እንደሚይዙ የጠቆመው የተመድ ሪፖርት፤ ባለፈው የፈረንጆች አመት 2016 ብቻ 5.6 ሚሊዮን ያህል የአለማችን ህጻናት በእነዚህ በሽታዎች ሳቢያ ለህልፈት መዳረጋቸውን አመልክቷል፡፡
ከአለማችን አካባቢዎች ከፍተኛው የህጻናት ሞት መጠን የሚመዘገበው ከሰሃራ በታች በሚገኙ የአፍሪካ አገራት እንደሆነ የጠቆመው ዘገባው፤ በ2016 በአገራቱ ከተወለዱ 1 ሺህ ህጻናት መካከል በአማካይ 79 ያህሉ ለሞት እንደተዳረጉ ጠቅሷል፡፡  
በሽታዎችን የመከላከሉና የመቆጣጠሩ ጥረት በአለማቀፍ ደረጃ ተጠናክሮ ካልቀጠለና ሁኔታዎች ባሉበት ከተጓዙ በመጪዎቹ 13 አመታት ጊዜ ውስጥ ዕድሜያቸው ከ5 አመት በታች የሆኑ ከ60 ሚሊዮን በላይ የአለማችን ህጻናት ለሞት ሊዳረጉ እንደሚችሉም ድርጅቱ ባወጣው ሪፖርት አስጠንቅቋል፡፡

Read 1116 times