Sunday, 05 November 2017 00:00

ትራኮን የሂስ፣ ጉባኤና የመፅሀፍት አውደ ርዕይ ይከፈታል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

እነሆ መፅሀፍ መደብር፣ ሊትማን ቡክስና ክብሩ መፅሀፍት መደብር በመተባበር በየወሩ መጨረሻ ባሉት ቅዳሜና እሁድ የሚያዘጋጁት የመፅሀፍ ሂስ ጉባኤና አውደ ርዕይ የዛሬ ሳምንት ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ ጥቁር አንበሳ ት/ቤት ፊት ለፊት በሚገኘው ትራኮን ህንፃ ላይ ይከፈታል፡፡
“ሀሳብን በሀሳብ መፈተን” በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው በዚህ የሂስ፤ ጉባኤና አውደ ርዕይ ላይ “የአለቃ ዓፅመ ጊዮርጊስ ገብረ-መሲህ ድርሰቶች (የኦሮሞ ታሪክ ከ1500-1900) የተሰኘው መፅሐፍ ለሂስ የተመረጠ ሲሆን መፅሀፉ በ19ኛው ክ/ዘመን ከተፃፉ መፅሀፍቶች መካከል የአገራችንን የ400 ዓመታት ታሪክና በተለይም የኦሮሞን ህዝብ ታሪክና ባህል በስፋት የሚያስቃኝ ነው ተብሏል  ለሂስና ለውይይት የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክና ሥነ-ጥበባት መምህር አቶ አበባው አያሌው እንደሆኑም የአውደርዕዩ ዝግጅት አስተባባሪ አቶ በፍቅሩ ዳኛቸው ገልፀዋል፡፡ ቅዳሜና እሁድ አውደርዕዩን የሚጎበኙ የመፅሀፍት እቁብን ጨምሮ ከ25 እስከ 50 በመቶ ቅናሽ የተደረገባቸው መፅሀፍት መግዛት እንደሚችሉ ተጠቁሟል፡፡

Read 3256 times