Monday, 13 November 2017 10:09

የቢን ላደን ልጅ አሜሪካን እንዲበቀሉለት ለጂሃዲስቶች ጥሪ አቀረበ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በአሜሪካ መንግስት አደንና ክትትል ከ6 አመታት በፊት በፓኪስታኑ አቡታባድ የተገደለው የአልቃይዳው መሪ የኦሳማ ቢንላደን ልጅ ሃማዝ፤ ጂሃዲስቶች በአሜሪካ ላይ ከፍተኛ የሽብር ጥቃት በመፈጸም የአባቱን ግድያ እንዲበቀሉለት ሰሞኑን ባወጣው የድምጽ መልዕክት ጠይቋል፡፡
ሃማዝ ቢን ላደን፤ “ጂሃዲስቶች በአሜሪካውያን በተለይ ደግሞ አባቴን ለመግደል በተደረገው የግፍ ዘመቻ ተሳታፊ በሆኑት ላይ ሁሉ በቻሉት መንገድ የሽብር ጥቃት በመፈጸም እንዲበቀሉልኝ እጠይቃለሁ” ሲል በአልቃይዳ የፕሮፓጋንዳ ማሰራጫዎች በኩል ባስተላለፈው መልዕክት መናገሩን ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግቧል፡፡
“አባቴ የጂሃድን መንፈስ የቀየረ ጀግና ሰማዕት ነው” በማለት ቢን ላደንን ያወደሰው የ28 ዓመቱ ሃማዝ፤ 25 ደቂቃ ያህል እርዝመት ባለው የድምጽ መልዕክቱ፣ የአፍጋኒስታኑን ታሊባን ቢያደንቅም አይሲስን በተመለከተ ግን ምንም ነገር አለማለቱን ዘገባው አመልክቷል፡፡
አሜሪካ በ2011 ቢን ላደንን በገደለችበት ወቅት የሃማዝ ወንድም ካሊድ መገደሉን ያስታወሰው ዘገባው፤ የአሜሪካው የስለላ ተቋም ሲአይኤ ባለፈው ሳምንት ከዚህ በፊት ታይተው የማይታወቁ ከቢን ላደን ጋር ተያያዥነት ያላቸውን በርካታ መረጃዎች ይፋ ማድረጉንም አስታውሷል፡፡

Read 1908 times