Print this page
Monday, 13 November 2017 10:01

የዓለም የጤና ድርጅት፤ ቡና እና ሞባይል ለካንሰር እንደሚያጋልጡ በመዋሸት ተወነጀለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  የዚምባቡዌን መሪ የጤና አምባሳደር አድርጎ በመምረጡ ዓለማቀፍ ውግዘት የገጠመውና የሾማቸውን ሙጋቤን ባፋጣኝ ከሻረ አንድ ወር ያልሞላው የዓለም የጤና ድርጅት፤ ቡና፣ ሞባይልና የታሸጉ የስጋ ምርቶች ለካንሰር በሽታ ያገልጣሉ የሚል ሃሰተኛ የጥናት ውጤት ይፋ አድርጓል በሚል አዲስ ውንጀላ ቀርቦበታል፡፡
ሮይተርስ የዜና ወኪል የዓለም የጤና ድርጅት በቅርቡ ይፋ ባደረገው ካንሰርን የተመለከተ የጥናት ውጤት ላይ ባደረገው ጥልቅ ምርመራ፣ ጥናቱ ከመውጣቱ በፊት በነበረው ሰነድ ላይ ቡና፣ ሞባይልና የታሸጉ የስጋ ምርቶች ለካንሰር በሽታ ስለማጋለጣቸው ምንም አይነት ነገር አለመጠቀሱን ጠቁሞ፣ ድርጅቱ ባወጣው የመጨረሻ ይፋዊ ሰነድ ላይ ግን ለካንሰር ያጋልጣሉ ብሎ  አዛብቶ ማውጣቱን  ማረጋገጡን አስታውቋል፡፡
ይህን ተከትሎም ሁለት የአሜሪካ የኮንግረስ አባላት የአለም የጤና ድርጅት ቡና መጠጣት፣ ሞባይል መጠቀምና የታሸጉ የስጋ ምግቦችን መጠቀም ለካንሰር ስለማጋለጣቸው ተጨባጭ ማስረጃውን ይስጠን ሲሉ መጠየቃቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ ጉዳዩ በተቋሙ ተሰሚነት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ሊፈጥር ይችላል መባሉን አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1669 times
Administrator

Latest from Administrator