Monday, 13 November 2017 10:15

አዲሱ ሾፌር አልባ አውቶብስ ጉዞ በጀመረ በሰዓታት ውስጥ ተጋጨ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 የአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪው የደረሰበት እመርታ አንዱ መገለጫ እንደሆነ ሲነገርለት የነበረው አዲሱ ሾፌር አልባ አውቶብስ፤ በአሜሪካ ላስቬጋስ ውስጥ 15 መንገደኞችን አሳፍሮ የመጀመሪያውን የሙከራ ጉዞ በጀመረ በሰዓታት ጊዜ ውስጥ በአቅራቢያው በቀስታ ሲጓዝ ከነበረ የባለሾፌር የጭነት መኪና ጋር መጋጨቱ ተነግሯል፡፡
በአሜሪካ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ መኪኖች በሚንቀሳቀሱበት ጎዳን ላይ የሙከራ ጉዞ በማድረግ የመጀመሪያው ነው የተባለውና ናቪያ የተባለው ታዋቂ የፈረንሳይ የአውቶሞቲቭ ኩባንያ የምርምር ውጤት የሆነው ይህ ሾፌር አልባ አውቶቡስ፤ በድንቅ ፈጠራነቱ በመገናኛ ብዙሃን ተወድሶ ሳያበቃ፣ በሰዓት 25 ኪሎ ሜትር ፍጥነት በመጓዝ ላይ እያለ ግጭቱ እንደደረሰበት ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ ምንም እንኳን ክስተቱ የብዙዎችን ትኩረት ቢስብም፣ አደጋው ቀላል ግጭት እንደሆነና በተሳፋሪዎች ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለመድረሱን የላስ ቬጋስ ከተማ ቃል አቀባይ መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡
ትኩረት ያገኘው ሾፌር አልባው አውቶቡስ ቢሆንም፣ በወቅቱ በአካባቢው የነበሩ የትራፊክ ፖሊሶች ግን፣ “ሾፈር አልባው አውቶብስ በአግባቡ እየተጓዘ እያለ አቅጣጫውን ስቶ አደጋውን ያስከተለው ባለሾፌሩ የጭነት መኪና ነው” ሲሉ ለሾፌሩ የቅጣት ወረቀት መቁረጣቸውንም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 3242 times