76ኛው ግጥም በጃዝ የኪነ-ጥበብ ምሽት የፊታችን ረቡዕ ከቀኑ 11፡30 ጀምሮ በራስ ሆቴል ይካሄዳል፡፡ ገጣሚና ተርጓሚ ነቢይ መኮንን፣ አርቲስት ፍቃዱ ተ/ማሪያም፣ አርቲስት ጌትነት እንየውና መንግስቱ ዘገዬ የግጥም ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን በዲያቆን ዳንኤል ክብረት ዲስኩር እንደሚቀርብ ገጣሚ ምስራቅ ተረፈ ገልፃለች፡፡
በፕሮግራሙ ላይ በዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ የተደረሰ “ደብተራው” የተሰኘ አጭር ተውኔት በአርቲስት ሽመልስ አበራና በእታፈራሁ መብራቱ ትወና ለታዳሚ የሚቀርብ ሲሆን ገጣሚና ተርጓሚ ጋዜጠኛ ነቢይ መኮንን ሰሞኑን ከዚህ ዓለም በሞት ስለተለየው ገጣሚና የፍልስፍና ሊቅ ሰለሞን ደሬሳ ይናገራል ተብሏል።