Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 14 April 2012 12:36

የሳዑዲ አየር መንገድ 43 የበረራ አስተናጋጆችን ቀጠረ 1ሺ ተወዳድረዋል፤ ደሞዛቸው 20ሺ ብር ነው ተብሏል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የሳዑዲ አረቢያ አየር መንገድ ለመጀመሪያ ጊዜ ከኢትዮጵያ የበረራ አስተናጋጆችን ለመቅጠር ሲያወዳድር የቆየ ሲሆን፤ ለአንደኛ ዙር 43 ሴቶች መርጦ የቅጥር ሂደት እንደጀመረ ሰሞኑን ገለፀ።እጩዎቹ የበረራ አስተናጋጆች ለወር ያህል ስልጠና ከወሰዱ በኋላ ስራ እንደሚጀምሩ፤ በአዲሱ የራዲሰን ሆቴል በተዘጋጀው የትውውቅ ግብዣ ላይ ተነግሯል። የቅጥር ፎርም የሞሉት እጩ የበረራ አስተናጋጆች፤ በሳዑዲ አረቢያ የጤና ምርመራ ካካሄዱ በኋላ ወደ ስልጠና እንደሚገቡ የገለፁት የአየር መንገዱ የስራ ሃላፊ፤ የበረራ አስተናጋጆቹ መነሻ ደሞዝ 880 ዶላር እንደሆነና ከ300 ዶላር በላይ ተጨማሪ አበል እንደሚያገኙ ተናግረዋል።

በጥቅሉ ወደ 20 ሺ ብር ገደማ ይሆናል። የጤና፣ የትራንስፖርት እና የመኖሪያ ቤት አገልግሎቶችን ጨምሮ፤ የበረራ አስተናጋጆቹ የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች ከአየር መንገዱ እንደሚያገኙም ሃላፊው ተናግረዋል።አየር መንገዱን በመወከል የቅጥር ውድድሩን ሲያከናውኑ የነበሩት የካቤ ዋና ስራአስኪያጅ አቶ ሁሴን ሰኢድ በበኩላቸው፤ የበረራ አስተናጋጆቹ በብቃት ስራቸውን እንደሚወጡ እምነታቸው መሆኑን ጠቅሰው፤ የሁለቱም አገራት አምባሳደሮች ናችሁ ብለዋል። አየር መንገዱ ስድሳ የበረራ አስተናጋጆችን ከኢትዮጵያ እንደሚቀጥር ካሁን ቀደም ተዝግቦ እንደነበር ይታወሳል።አሁን የተካሄደው የቅጥር ውድድር የመጀመሪያ ዙር እንደሆነና በሁለቱ አገራት ግንኙነት አዲስ መንገድ የሚከፍት መሆኑን የተናገሩት አቶ ሁሴን ሰኢድ፤ ይህን ግንኙነት የሚያስፋፉ ተጨማሪ ዙሮች ይቀጥላሉ ብለዋል።በዚሁ ውድድር አንድ ሺ ሴቶች የተሳተፉ ሲሆን፤ አሁን ለቅጥር ፎርም የሞሉት 43 ሴቶች የሳዑዲ ጉዟቸው መቼ እንደሚሆን ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ይነገራችኋል ተብለዋል።

 

 

Read 1335 times Last modified on Saturday, 14 April 2012 12:39