የደራሲ ሰዓዳ መሀመድ “ደባሎቼና ሌሎችም” የተሰኘ አዲስ የአጭር ልቦለዶች ስብስብ መፅሀፍ ገበያ ላይ ዋለ፡፡ ሰባት አጫጭር ልቦለዶችን ያካተተው መፅሀፉ፤ ከሰባቱ አምስቱ የደራሲዋ ስራዎች ከዚህ ቀደም ከሌሎች ደራሲያን ስራዎች ጋር በጋራ ታትመው የነበሩ ሲሆን ሁለቱ አዲስ እንደሆኑ ታውቋል፡፡ በ130 ገፆች የተቀነበበው መፅሀፉ፤ በ60 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡
በሌላ በኩል፣ የፊታችን አርብ ህዳር 15 ቀን 2010 ዓ.ም ከ11፡30 ጀምሮ “ፍቅር የተራበ” የተሰኘው ቴአትር በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት የሚታይ ሲሆን ገቢው በህመም ላይ ለምትገኘው ደራሲ ሰዓዳ መሀመድ የሚውል በመሆኑ ሁሉም ሰው ቴአትሩን በመታደም ደራሲዋን እንዲረዳ ጥሪ ቀርቧል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና