ሶስት የተለያየ መጠን ያላቸው የሲኒማ አዳራሾችን የያዘውና ብስራተ-ገብርኤል በሚገኘው ላፍቶ ሞል ላይ የተደራጀው “እንይ ሲኒማ”፤ ዛሬ ከቀኑ 10፡00 ጀምሮ በይፋ ተመርቆ ስራ እንደሚጀምር፣ የሲኒማ ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ፍሬዘር ተሾመ ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡ለሲኒማ ቤቱ የምርቃት ስነ-ስርዓት “እርቅ ይሁን” የተሰኘው ፊልም ለእይታ ይበቃል ተብሏል፡፡ ሲኒማ ቤቱ፡- 3 አዳራሾች ያሉት ሲሆን ትልቁ አዳራሽ ሲኒማ 1፡- 240 ወንበሮች፣ ሲኒማ 2፡- (መካከለኛው) 160 ወንበሮች እና ሲኒማ 3፡- (ትንሹ) 145 ወንበሮች እንዳሉት አቶ ፍሬዘር ገልፀዋል፡፡
ዘወትር ቅዳሜና እሁድ ሲኒማ ቤቱ የህፃናት ፊልምና መዝናኛዎችን እንደሚያዘጋጅ የተጠቆመ ሲሆን ከ3 ወራት በኋላም ጥራት ያላቸው ቴክኖሎጂዎችን ገጥሞ፣ የሆሊውድ ፊልሞችን ለእይታ እንደሚያበቃ ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
በምርቃት ስነ -ስርዓቱ ላይ የኪነ-ጥበብ ባለሞያዎች፣ ታዋቂ ሰዎች፣ የባህልና ቱሪዝም ሀላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይታደማሉ ተብሏል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና