Monday, 20 November 2017 00:00

የዳቬንቺ ስዕል ክብረ ወሰን ባስመዘገበ 450 ሚ. ዶላር ዋጋ ተሸጠ

Written by 
Rate this item
(8 votes)


    ታዋቂው ሰዓሊ ሊዮናርዶ ዳቬንቺ ከ500 አመታት በፊት የሳለውና የእየሱስን ምስል የሚያሳየው ጥንታዊ ስዕል፣ ኒውዮርክ ውስጥ በተካሄደ ጨረታ በ450 ሚሊዮን ዶላር መሸጡና ሽያጩ ክብረ ወሰን የተመዘገበበት መሆኑ ተዘግቧል፡፡
“መድሃኒያለም” በመባል የሚታወቀውና የአንድ ግለሰብ ንብረት ሆኖ የቆየው ይህ ስዕል፤በ100 ሚሊዮን ዶላር መነሻ ዋጋ ለጨረታ ቢቀርብም በስተመጨረሻ በ450 ሚሊዮን ዶላር ዋጋ ስሙ ላልተጠቀሰ አሸናፊ መሸጡን ክርስቲ የተባለው አጫራች ኩባንያ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
አንድ ሩስያዊ ግለሰብ በ2013 ዓ.ም በ127 ሚሊዮን ዶላር ገዝቶት የግል ንብረቱ አድርጎት የነበረው ይህ ጥንታዊ ስዕል፤ ሰሞኑን የተሸጠበት ዋጋ፣ እስካሁን ድረስ በዓለማችን የስዕል ሽያጭ ታሪክ ከፍተኛው እንደሆነ የዘገበው ቢቢሲ፤ ከዚህ በፊት ከፍተኛ ዋጋ የተሸጠው ስዕል የታዋቂው ሰዓሊ ቫንጎ ስዕል እንደነበረም አስታውሷል፡፡

Read 5874 times