Print this page
Sunday, 26 November 2017 00:00

ህንዳዊው ሚኒስትር “ካንሰር የሚይዘው ሃጢያተኛ ሰው ነው” አሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  ልጆች በወላጆቻቸው ሃጢያት ለከፋ በሽታ ሊጋለጡ ይችላሉ ብለዋል

   የህንድ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ሂማንታ ቢስዋ ሳማራ፤ የካንሰር በሽታ የሚያጠቃው ሃጢያት የሰራ ሰውን ነው ሲሉ በይፋ መናገራቸውን ተከትሎ፣ በሚኒስትሩ ንግግር የተቆጡ በርካታ ህንዳውያን የካንሰር ታማሚዎችና ቤተሰቦቻቸው ተቃውሟቸውን ማሰማታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ሚኒስትሩ ባለፈው ረቡዕ ጉዋሂቲ በተባለቺው የህንድ ከተማ፣ ህዝብ በተሰበሰበበት አደባባይ ባደረጉት ንግግር፤ ሰዎች ራሳቸው በሰሩት የሃጢያት ድርጊት ምክንያት በካንሰር ከመያዛቸው ባለፈ፣ በወላጆቻቸው ሃጢያት ሳቢያም ለሌሎች ተመሳሳይ አደገኛ በሽታዎች ሊጋለጡ እንደሚችሉም በእርግጠኝነት ተሞልተው መናገራቸውን ዘገባው ገልጧል፡፡
“ኦል ኢንዲያ ዩናይትድ ዲሞክራቲክ ፍሮንት” የተባለው የአገሪቱ ታዋቂ ፓርቲን ጨምሮ የተለያዩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች፤ ሚኒስትሩ በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቁ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፣ ሰውዬው ይህን ሳይንሳዊ መሰረት የሌለው ንግግር ያደረጉት የካንሰርን ስርጭት ለመግታት አለመቻላቸውን ባልሆነ መንፈሳዊ ሰበብ ለመሸፋፈን በማሰብ ነው ብለዋል፡፡
ጉዳዩ ህንዳውያንን ጨምሮ በአለማቀፍ ደረጃ በማህበራዊ ድረገጾች ተጠቃሚዎች ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ እንደገጠመው የጠቆመው ዘገባው፤ በአገሪቱ በካንሰር የሚጠቁ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ እንደሚገኝና በመጪዎቹ 3 አመታት ውስጥ በ25 በመቶ ሊያድግ እንደሚችል ጥናቶች እንደሚጠቁሙ ገልጧል፡፡

Read 1712 times
Administrator

Latest from Administrator