ታዋቂው የደቡብ ኮርያ የኤሌክትሮኒክስ አምራች ኩባንያ ሳምሰንግ፣ ጋላክሲ ኤክስ የተባለውን እንደ ፕላስቲክ የሚታጠፍና የሚዘረጋ ልዩ ስማርት ፎን አምርቶ በመጪው አንድ ወር ጊዜ ውስጥ በገበያ ላይ እንደሚያውል አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
የመሸጫ ዋጋው ምን ያህል እንደሆነ እስካሁን በይፋ ባይታወቅም ከነባሮቹ የጋላክሲ ምርቶች ውድ እንደሚሆን የተገመተው ጋላክሲ ኤክስ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ ገበያ ላይ የሚውለው በደቡብ ኮርያ ሲሆን በቀጣይም በብዛት ተመርቶ ለአለማቀፍ ገበያ እንደሚቀርብ ተነግሯል፡፡
ይህንን ልዩ የሆነ ተጣጣፊ ሞባይል እንደሚያመርት ለአመታት ሲነገርለት ቢቆይም ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በይፋ መረጃ ሳይሰጥ የቆየው ኩባንያው፤ ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ አዲሱን ምርቱን በፈረንጆች አዲስ አመት መጀመሪያ ለገበያ እንደሚያቀርብ ማስታወቁን የጠቆመው ዘገባው፤ሳምሰንግ ከዚህ በተጨማሪም አዲሱን ጋላክሲ 9 የሞባይል ምርቱን በመጪው የካቲት ወር ላይ ለገበያ እንደሚያበቃ መግለጹን አመልክቷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ