Print this page
Sunday, 26 November 2017 00:00

ቢዮንሴ የዓመቱ የአለማችን ከፍተኛ ተከፋይ ድምጻዊት ሆናለች

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ድምጻዊቷ በዓመቱ በድምሩ 105 ሚ. ዶላር አግኝታለች

    አሜሪካዊቷ ድምጻዊት ቢዮንሴ ኖውልስ በፈረንጆች አመት 2017 ከፍተኛውን ክፍያ ያገኘች ቁጥር አንድ የአለማችን ሴት ድምጻዊት መሆኗን በሳምንቱ መጀመሪያ ባወጣው መረጃ ይፋ ያደረገው ፎርብስ መጽሄት፤ድምጻዊቷ በአመቱ ከአልበም ሽያጭና ከሙዚቃ ኮንሰርት በድምሩ 105 ሚሊዮን ዶላር አግኝታለች ብሏል፡፡
በአመቱ 69 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ያገኘቺው እንግሊዛዊቷ ድምጻዊት አዴል፣ሁለተኛዋ የአለማችን ከፍተኛ ተከፋይ ሴት ድምጻዊት ስትሆን፣ ባለፈው አመት በአንደኛ ደረጃ ላይ የነበረቺው ቴለር ስዊፍት ዘንድሮ በ44 ሚሊዮን ዶላር ወደ ሶስተኛነት ዝቅ ማለቷን ፎርብስ አስታውቋል፡፡
ሴሊን ዲዮን በ42 ሚሊዮን ዶላር፣ ጄኔፈር ሎፔዝ በ38 ሚሊዮን ዶላር፣ ዶሊ ፓርተን በ37 ሚሊዮን ዶላር፣ ሪሃና በ36 ሚሊዮን ዶላር፣ ብሪትኒ ስፒርስ በ34 ሚሊዮን ዶላር፣ ኬቲ ፔሪ በ33 ሚሊዮን ዶላር፣ ባርባራ ስትሪሳንድ በ30 ሚሊዮን ዶላር እንደ ቅደም ተከተላቸው ከአራተኛ እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡
ፎርብስ ዝርዝሩን ያወጣው በአጠቃላይ በሙዚቃው ኢንዱስትሪ ውስጥ የተሰማሩ ሴቶችን የአመቱ አጠቃላይ ገቢ በማጥናት ቢሆንም፣ ሁሉም በሚባል ደረጃ ከፍተኛ ተከፋይ ሆነው የተገኙት የዘርፉ ከዋክብት ድምጻውያን ናቸው ተብሏል፡፡

Read 3083 times
Administrator

Latest from Administrator