Saturday, 25 November 2017 10:25

በሰሜን ኮርያ ተሰባስቦ መዝፈንና መጠጣት ተከልክሏል

Written by 
Rate this item
(5 votes)

ከዚህ በፊትም ዜጎች የእናቶች ቀንን እንዳያከብሩ ተከልክለው ነበር

   የሰሜን ኮርያ መንግስት የአገሪቱ ዜጎች በቤታቸውም ሆነ በመዝናኛ ስፍራዎች በጋራ ተሰባስበው እየዘፈኑና እየጠጡ እንዳይዝናኑ የሚከለክል አዲስ መመሪያ ማውጣቱን ዘ ኢንዲፔንደንት ባለፈው ማክሰኞ ባወጣው ዘገባ አመልክቷል፡፡
የአገሪቱ መንግስት ዜጎቹን በጋራ ከመዝናናት የሚያግደውን ይህንን መመሪያ ማውጣቱን በተመለከተ መረጃ እንዳገኘ የደቡብ ኮርያ ብሄራዊ የስለላ ተቋም፣ ባለፈው ሰኞ በሰጠው መግለጫ ማስታወቁን ዘገባው አመልክቷል፡፡
የሰሜን ኮርያ መንግስት በዜጎች ላይ ተመሳሳይ ክልከላዎችን ሲያደርግ ይህ የመጀመሪያው አይደለም ያለው ዘገባው፣ ባለፈው ሐምሌ ወር ላይም እጅግ ተወዳጁንና በአገሪቱ ዜጎች ዘንድ ለረጅም አመታት በስፋት ሲከበር የኖረውን የ”ፒንግያንግ የቢራ ፌስቲቫል” እንዳይከናወን ማገዱን አስታውሷል፡፡
ሰሜን ኮርያውያን በአለማቀፍ ደረጃ በሚከበረው “የእናቶች ቀን” በዓል ወቅት ለእናቶቻቸው ያላቸውን ፍቅርና ክብር እንዳይገልጹ በመንግስታቸው ክልከላ እንደተደረገባቸው ያስታወሰው ዘገባው፤ የአገሪቱ መንግስት ይህንን እርምጃ የወሰደው “ድርቅ በተከሰተበት ወቅት ቢራ መጠጣት አግባብ አይደለም” በሚል እንደነበርም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 2708 times