ሚዩዚክ ሜይዴይ፣ ከኢትዮጲስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር፣ ነገ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ “ኢትዮጵያዊነት አሰባሳቢ ማንነት በአንድ አገር ልጅነት” በተሰኘው የደራሲ የሱፍ ያሲን መፅሐፍ ላይ በብሄራዊ ቤተ-መፃህፍትና ቤተ- መዛግብት ኤጀንሲ (ወመዘክር) አዳራሽ ውይይት ያካሂዳል፡፡ ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት የፖለቲካል ሳይንስ ባለሙያው አቶ ኤፍሬም ቦተሬ ሲሆኑ ፍላጎት ያለው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ ተጋብዟል፡፡