“ለምን እቀናለሁ” እያልኩ አስባለሁ
ሰርክ እጨነቃለሁ
“ከሚሊዮን አትሌት ከህይወት ማራቶን
ሁሌም ከፊት ልሮጥ እንዴት እችላለሁ፡፡
እያልኩ አስባለሁ
ግን የሆነ ሆኖ…
ከፊት በሚሮጠው ዛሬም እቀናለሁ…
እኒህ የግጥም ስንኞች የተመዘዙት ሰሞኑን አንባቢያን እጅ ከደረሰው የገጣሚ ዳንኤል ሥዩም መንገሻ “ፍቅር እና ሽንቁር” የተሰኘ የግጥም መድበል ውስጥ “ቃየንን ፍለጋ” በሚል ርዕስ ከቀረበው ግጥም ነው፡፡ በ84 ገፆች የተቀነበበው መድበሉ፤ 46 ግጥሞችን ያካተተ ሲሆን በ40 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡