በአጼ ኃይለስላሴ ዘመን ሀገራችንን በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነትና በጠቅላይ ሚኒስትርነት ስላገለገሉት ለ ጸሀፌ-ትእዛዝ አክሊሉ ሀብተ-ወልድ የሚተርክ የ72 ደቂቃ ቪድዮ በዲቪዲ የተዘጋጀ ሲሆን በነገው ዕለት ከ8 ሰዓት ጀምሮ በራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ አዳራሽ ይመረቃል ተብሏል፡፡ አክሊሉ ሀብተወልድ ሀገራችን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከዛሬ 70 አመት በፊት አባል ስትሆን ትልቅ የዲፕሎማሲ ስራ የሰሩ ሰው መሆናቸው ይታወቃል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንዲመሰረት ጉልህ ሚና ያበረከቱት አክሊሉ፤ በሀገራችን ከህገ-መንግስት አንስቶ በርካታ ደንቦችና ህጎች እንዲሻሻሉ በር የከፈቱ ምሁር ናቸው፡፡ የዘጋቢ ፊልሙ አዘጋጅ ጋዜጠኛ እዝራ እጅጉ ነው፡፡
Saturday, 09 December 2017 13:50
የፀሃፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ ዲቪዲ ነገ ይመረቃል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና