Sunday, 10 December 2017 00:00

“በእናት መንገድ” ፊልም ሰኞ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 በደራሲና ዳይሬክተር በሀይሉ ዋሴ (ዋጄ) ተፅፎ የተዘጋጀውና በእውነት መልቲ ሚዲያ ፕሮዳክሽን ተዘጋጅቶ፣ በኧርሊ ኤ. ኤም መልቲ ሚዲያ የቀረበው “በእናት መንገድ” የተሰኘ ፊልም ከነገ በስቲያ ሰኞ ከቀኑ 11፡30 ጀምሮ በብሄራዊ ቴአትር እንደሚመረቅ አስተባባሪው ኢጋ ሚዲያ ኮሚዩኒኬሽን አስታወቀ፡፡
የድራማ ዘውግ ያለውና 1፡35 ርዝመት ያለው ፊልሙ፣ ተሰርቶ ለመጠናቀቅ 1 ዓመት ጊዜ እንደፈጀ የተነገረ ሲሆን 850 ሺ ብር እንደወጣበትም ተገልጿል፡፡  በፊልሙ ላይ ደሞዝ ጎሽሜ፣ ሜላት ሰለሞን፣ መስፍን ሀይለየሱስ፣ ብርሀኔ ገብሩ፣ አሸናፊ ዋሴ፣ ለምለም አበራ፣ ሰለሞን ተስፋዬና ሌሎችም የተወኑበት ሲሆን በሜላት ሰለሞን ፕሮዱዩስ መደረጉ ታውቋል፡፡

Read 1954 times