Saturday, 23 December 2017 09:00

ርዕዩን ነጠቋት …!

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ርዕዩን ነጠቋት …!

ኢትዮጵያን ሲያስባት፣ ከዘመናቷ ጠልቆ፣
ጭፍን ሐሳቧ ውስጥ፣ እንዳሸመቀች አውቆ፣
ነጯን ከጥቁር ተማጥቆ፣
ግራጫ ዶሴዋን ጠብቆ፣
የ’ኛን ዐስርት ዓመታት፣ በደቂቃ እድሜው
እየኖረው፣
ዓለም አቀፉን ዕውነታ፣ ሀገሩ በልማድ
ስትወቅረው …
ዘመኗን በ’ውቀት አሰፋ፡፡ የነቢይን
ገቢር ወርሶ፣
የኢዮብን ትዕግስት ጽናት፣ ከሰለሞን
ጥበብ ተውሶ፡፡
ርዕዩን ከአድማስ አሻግሮ፣ አምዶቿን
አለት ላይ ተክሎ፣
የልቡን ትጋት አክሎ፣
ሐሳቡን በጥበብ ሸጠ፤ ዕውቀትን
በአዲስ አብቅሎ፡፡
ዛሬ …
ርዕዩን ማነገት ታክቷት፣ እንደ ሰካራም ባልቴት
ሀገሩ ስትንገዳገድ፣
ነጻ ፈቃዷን ሳትኖረው፣ ድንቁርና ሠልጥኖባት
ስትዋጅ መጥፊያዋን መንገድ፣
ልዕልናዋም ረክሶ፣ እርቀ ሰላሙ ተሰውሮባት
ዘረ ሰቧም ተኳረፈ፤
ደም ፍላቷ ተንተክትኮ፣ አኬልዳማዋ ከሚታየው
እንኳንም እሱ ቀድሞ አረፈ፡፡

                                                                          ገዛኸኝ ፀ. ጸጋው

Read 1328 times Last modified on Saturday, 23 December 2017 09:07