አሴ!
ዛሬም አንረሳህም፣ እናስታውሳለን
አይሞትም ፈገግታህ
ብርሃን ይረጫል፣ተስፋችንን ያውቃል!
የዘራኸው አለ፣ ዘመን ቆጥሮ ዘልቋል፡፡
አሥራ ሶስት ዓመትክን ዛሬም ይዘክራል!
አሴ!
ያው እንደምታውቀው
ሥልጣንም ደክሞታል
የፀናው ሲጠና፣ የደከመው ወድቋል!
ወትሮም እንደዚያው ነው
አንደኛው ሲለሰን፣ ስንጥቅ ነው ሌላኛው
አገርህ ያችው ናት
ባንድ ምህዋር ላይ፣ ስትዞር የምታቃት!
እያደር ስትከር፣ ውል የሚጠፋባት
አሴ አላጣሃትም-
አገርህ ያችው ናት!
(ለአሰፋ ጐሣዬ 13ኛ ዓመት)
ነ.መ
Published in
ጥበብ