Print this page
Monday, 25 December 2017 00:00

የኡጋንዳውን መሪ ስልጣን 40 አመታት የሚያደርሰው ህግ ጸደቀ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 የኡጋንዳ ፓርላማ የአገሪቱን ፕሬዚዳንት የዕድሜ ገደብ የሚያስቀረውንና አምስት አመት የነበረውን አንድ የስልጣን ዘመን ወደ ሰባት አመት ከፍ በማድረግ፣ ከ30 ዓመት በላይ አገሪቱን የገዙትን ዮሪ ሙሴቬኒንን የስልጣን ቆይታ ከአርባ አመታት በላይ የሚያደርሰውን የህገ መንግስት ማሻሻያ አጽድቆታል፡፡
ሙሴቬኒ በ2021 በሚካሄደው ቀጣዩ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ወቅት 77 አመት የሚሆናቸው ሲሆን ህጉ ግን ለመሪነት መወዳደር የሚችለው ዕድሜው ቢበዛ 75 አመት የሆነ ነው ይላል፡፡ ፕሬዚዳንቱ በምርጫው ለመወዳደርና ስልጣናቸውን ለማራዘም ሲሉ ህጉ እንዲሻሻል ባቀረቡት ሃሳብ ላይ ለሶስት ቀናት በከፍተኛ ሁኔታ የተከራከሩት የፓርላማ አባላቱ፤ በስተመጨረሻም ባለፈው ረቡዕ በሰጡት የድጋፍ ድምጽ እንዳጸደቁት ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
የፓርላማው አባላት በጉዳዩ ዙሪያ ያደረጉትን የተራዘመ ክርክር ሲያጠናቅቁ በሰጡት ድምጽ፣ በ315 ድጋፍና በ62 ተቃውሞ በአብላጫ ድምጽ የህገ መንግስት ማሻሻያውን ማጽደቃቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ ይህን ተከትሎም የተቃዋሚ ፓርቲዎች ደጋፊዎች ተቃውሞና ብጥብጥ ሊያስነሱ ይችላሉ ተብሎ በመሰጋቱ፣ ፖሊስ በተጠንቀቅ እንዲቆም መታዘዙን አመልክቷል፡፡
ማሻሻያው የሙሴቬኒን ስልጣን ለማራዘም ሆን ተብሎ የተደረገ ነው በሚል ሃሳቡን ሲቃወሙ የነበሩ ስድስት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አባላት ከፓርላማው መባረራቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ ባለፈው መስከረም ወር ላይ ጉዳዩ ለፓርላማ ቀርቦ በተደረጉት ውይይቶች ላይ በተፈጠሩ ውዝግቦች የፓርላማው አባላት በወንበር እየተወራወሩ እስከመፈነካከት ደርሰው እንደነበርም አስታውሷል።
ረቂቅ ሃሳቡ ለፓርላማ ውሳኔ ከቀረበ ቆየት ቢልም፣ በአፋጣኝ ድምጽ ሊሰጥበት ያልቻለው የአገሪቱ ህግ አውጪዎች፤ ውሳኔውን የሚያጸድቅ የድጋፍ ድምጽ ለመስጠት ከሙሴቬኒ መንግስት ለእያንዳንዳቸው 83 ሺህ ዶላር በሙስና መልክ እንዲከፈላቸው በመጠየቃቸው ነው መባሉን ባለፈው ሳምንት ኦልአፍሪካን ኒውስን ጠቅሰን መዘገባችን  ይታወሳል፡፡

Read 1856 times
Administrator

Latest from Administrator