Print this page
Tuesday, 26 December 2017 00:00

ለእንግሊዛውያን ፈጣን ኢንተርኔት ማግኘት ህጋዊ መብት ሊሆን ነው

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 የእንግሊዝ መንግስት ፈጣን የብሮድባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት ማግኘት በመጪዎቹ ሶስት አመታት ጊዜ ውስጥ የሁሉም የአገሪቱ ዜጎችና ተቋማት ህጋዊ መብት እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡
የቴሌኮም አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ የአገሪቱ ተቋማት የብሮድባንድ ኢንተርኔት እንዲያቀርቡላቸው ለሚጠይቋቸው ሁሉም ዜጎችና ተቋማት ቢያንስ እስከ 10 ሜጋ ባይት በሰከንድ ፍጥነት ያለው የኢንተርኔት አገልግሎት መስጠት ግዴታቸው እንደሚሆን የአገሪቱ መንግስት አስታውቋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በተለይ በአገሪቱ የገጠር  አካባቢዎች የሚገኙ ከ1 ሚሊዮን በላይ የግለሰብ መኖሪያ ቤቶች፣ የፈጣን ኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚ እንዳልሆኑ የጠቆመው ዘገባው፤ እ.ኤ.አ ከ2020 ጀምሮ ግን ሁሉም የአገሪቱ ዜጎች የፈጣን ብሮድባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት ማግኘት ህጋዊ መብታቸው እንደሚሆንና ተገቢውን አገልግሎት በአፋጣኝ በማይሰጡ የቴሌኮም ተቋማት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ መነገሩንም አመልክቷል፡፡
እንግሊዝ በብሮድባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት ፍጥነት ከሌሎች የአለማችን ያደጉ አገራት ጋር ሲነጻጸር፣ እጅግ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ እንደምትገን የጠቆመው ዘገባው፤ በጃፓን 97 በመቶ ያህሉ የኢንተርኔት አገልግሎት በሙሉ ፋይበር መስመር የሚሰሩ ሲሆን በእንግሊዝ ግን በተመሳሳይ ሁኔታ የሚሰሩት 3 በመቶ ብቻ መሆናቸውንም አክሎ ገልጧል፡፡


Read 2283 times
Administrator

Latest from Administrator