Monday, 01 January 2018 00:00

“ገናን ከልጆች ጋር” የመዝናኛ ፕሮግራም ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 አብርሀም ግዛው ኢንተርቴይመንት ከጄቲቪ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር “ገናን ከልጆች ጋር” የተሰኘ ልዩ የበዓል መዝናኛ ፕሮግራም ያቀርባል፡፡ ፕሮግራሙ በዋናነት በበዓል ወቅት ትኩረት የሚነፈጋቸውን ልጆች ታሳቢ ያደረገ ሲሆን የፕሮግራሙ ቀረፃ ሳር ቤት በሚገኘው “ኤስ ኦ ኤስ” የህፃናት መንደር ነገ የሚቀረፅ ሲሆን እንደ ሌባና ፖሊስ፣ ቅልብልቦሽ፣ እምቡሼ ገላ፣ የገና ጫዋታ፣ ገበጣ፣ ሱዚና ሌሎች ጨዋታዎች የሚካሄድ ሲሆን በልጆች ጉዳይ ላይ ውይይት፣ የልምድ ልውውጥና ልዩ የቤተሰብ ተሞክሮዎች ለታዳሚው እንደሚቀርቡ አዘጋጁ አብርሀም ግዛው ገልጿል፡፡
ፕሮግራሙም የገና በዓል ዕለት ከረፋዱ ከ3፡00እስከ 4፡30 በጂቲቪ ኢትዮጵያ እንደሚተላለፍ ታውቋል፡፡

Read 1150 times